ማሻ፣ ታህሳስ 27/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍኤም 103.8) በ20ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ እና ቼልሲ 1 አቻ ተለያይተዋል።
የማንቼስተር ሲቲን ግብ ቲጃኒ ሬንደርስ ሲያስቆጥር ለቼልሲ ደግሞ ኢንዞ ፈርናንዴዝ ከመረብ አሳርፏል።
አስቀድሞ በተደረጉ ጨዋታዎች ሊቨርፑል ከፉልሃም ሁለት አቻ ፣ማንቼስተር ዩናይትድ ከሊድስ ዩናይትድ እንዲሁም ቶተንሃም ሆትስፐር ከሰንደርላንድ በተመሳሳይ አንድ አቻ ተለያይተዋል፡፡
በሌላ የሊጉ ጨዋታዎች ኒውካስል ዩናይትድ ክሪስታል ፓላስን 2 ለ 0 እንዲሁም ብሬንትፎርድ ኤቨርተንን 4 ለ 2 በሆነ ውጤት ማሸነፋቸው ይታወቃል፡፡
More Stories
ኢትዮጵያ በአልማዝ ዮሀንስ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳልያ አስመዘገበች
ኢትዮጵያዊ በዳምጠው ከበደ ተጨማሪ ሜዳሊያ አገኘች
ቴፒ ከተማ እግር ኳስ ክለብ ደማቅ አቀባበል ተደረገለት