በታንዛኒያ አስተናጋጅነት በሚካሄደው ከ20 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ የሴካፋ ማጣሪያ ውድድር የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ለውድድሩ ቅድመ ዝግጅት ጥሪ የተደረገላቸው 40 ተጫዋቾችን በመያዝ ዛሬ ናሽናል ካምፒንግ እንደሚጀምር የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አሳውቋል።
የብሔራዊ ቡድኑን በዋና አሰልጣኝነት ቤንጃሚን ዚመር የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በሴካፋ ውድድር 3ኛ ደረጃን ይዞ እንዲያጠናቅቅና ከ22 ዓመታት በኋላ ለ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ እንዲያልፍ ያደረጉ ሲሆን በውድድሩም ቡድኑ ጠንካራ ተፎካካሪ በመሆን ለዓለም ዋንጫ ለማሳለፍ ከጫፍ አድርሰውት እንደነበር ይታወሳል።
በምክትል አሰልጣኝነት የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እና በተለያዩ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ታላላቅ ክለቦች ተጫውቶ ያሳለፈው ፍፁም ገብረማርያም የተሾመ ሲሆን በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እንዲሁም በፕሪምየር ሊግ እና ከፍተኛ ሊግ ክለቦች ተጫውቶ ያሳለፈውና በጅማ አባ ቡና እንዲሁም በመቻል (ከ17 ዓመት በታች ቡድን) በግብ ጠባቂ አሰልጣኝነት የሠራው ገመቹ በቀለ በግብ ጠባቂ አሰልጣኝነት የሚሠራ ይሆናል።
More Stories
አርሰናል 5 ተጨዋቾችን ያስመረጠበት የፒ ኤፍ ኤ የዓመቱ ምርጥ 11 ይፋ ተደረገ
ብሩኖ ፈርናንዴዝ የፒ ኤፍ ኤ የዓመቱ ምርጥ ተጨዋች ሽልማትን አሸነፈ
ቼልሲ የውድድር ዓመቱን በምዕራብ ለንደን ደርቢ ይጀምራል