ማሻ፣ ጥር 02/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍኤም 103.8) በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ባለው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ መርሐ ግብር ሴኔጋል ማሊን 1 ለ 0 በማሸነፍ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ገብታለች።
ምሽት 1 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ ሴኔጋል ኒጃይ ባስቆጠረው ግብ የግማሽ ፍጻሜ ተፋላሚ ለመሆን በቅታለች።
በጨዋታው የማሊው ቢሱማ በሁለት ቢጫ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል።
መርሐ ግብሩ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ቀጥሎ ሲካሄድ አዘጋጇ ሞሮኮ እና ካሜሩን የሚያደርጉት የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ ይጠበቃል።
ሞሮኮ ታንዛኒያን በማሸነፍ እንዲሁም ካሜሩን ደቡብ አፍሪካን በማሸነፍ ነው ለሩብ ፍፃሜ የደረሱት።
More Stories
አርሰናል ከ20 ዓመት በኋላ በሻምፒዮንስ ሊግ ለፍጻሜ ደረሰ
ማንቼስተር ዩናይትድ ሊቨርፑልን በማሸነፍ የሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎውን አረጋገጠ
ኬንያዊው አትሌት በሽልማት ተንበሸበሸ