August 26, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

አርሰናል 5 ተጨዋቾችን ያስመረጠበት የፒ ኤፍ ኤ የዓመቱ ምርጥ 11 ይፋ ተደረገ

በመካሄድ ላይ በሚገኝው የፕሮፌሽናል እግር ኳስ ተጨዋቾች ማህበር ሽልማት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ምርጥ 11 ይፋ ሲደረግ አርሰናል 5 ተጨዋቾችን በማስመረጠ ቀዳሚ ሆኗል።

ዴቪድ ራያ፣ ዴክለን ራይስ፣ ጋብርኤል ማጋሌሽ፣ ዊሊያም ሳሊባ እና ዩሪይን ቲምበር የተመርጡ የመድፍኞቹ ከዋክብት ናቸው።

ማንችስተር ሲቲ 4 ተጨዋቾች ሲያስመርጥ፣ ኧርሊንግ ሃላንድ፣ ራያ ን ቼርኪ፣ አንቱዋን ሴሜኒዮ እና ኒኮ ኦሪሊ ተካተዋል። ዩናይትድ ብሩኖ ፈርናንዴዝን ሲያስመርጥ ብሬንትፎርድ ደግሞ ኢጎር ቲያጎን አስመርጧል።