February 4, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

አስቶንቪላ ኖቲንግሃም ፎረስትን አሸነፈ

ማሻ፣ ታህሳስ 26/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍኤም 103.8) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 20ኛ ሳምንት መርሐ ግብር አስቶንቪላ ኖቲንግሃም ፎረስትን 3 ለ 1 አሸንፏል፡፡

ቀን 9 ሰዓት ከ30 በተረደገው ጨዋታ ኦሌ ዋትኪንስ እና ጆን ማክ ጊን (ሁለት) ለአስቶን ቪላ ግቦቹን ሲያስቆጥሩ ሞርጋን ጊብስ ዋይት የኖቲንግሃም ፎረስትን ብቸኛ ግብ ከመረብ አገናኝቷል።

ውጤቱን ተክትሎም አስቶንቪላ ነጥቡን ወደ 42 ከፍ አድርጓል።