
የሽግግር ፕሬዝዳንቱ ማሃማት ኢድሪስ ዴቢ በምርጫው የማሸነፍ ቅድመ ግምት ተሰጥቷቸዋል
ነዳጅ ሻጯ ሀገር በ1960 ከፈረንሳይ ነጻነቷን ካወጀች ወዲህ ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ማካሄድ አልቻለችም
ቻድ ለሶስት አመት ከቆየችበት ወታደራዊ አገዛዝ ለመውጣት ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ እያካሄደች ነው።
የመካከለኛው አፍሪካዋን ሀገር ለ30 አመት የመሩት ኢድሪስ ዴቢ በ2021 በአውደ ውጊያ ላይ ህይወታቸው ካለፈ በኋላ ልጃቸው ጀነራል ማህማት ኢድሪስ ዴቢ የሽግግር ጊዜ ፕሬዝዳንት ሆኖ በማገልገል ላይ መሆኑ ይታወቃል።
ጀነራል ማህማት በዛሬው እለት እየተካሄደ በሚገኘው ምርጫ እየተፎካከሩ ሲሆን፥ የማሸነፍም ቅድመ ግምት ተሰጥቷቸዋል።
8 ነጥብ 5 ሚሊየን መራጮች ድምጽ ለመስጠት በተመዘገቡበት ምርጫ ጠቅላይ ሚኒስትር ሱኬስ ማስራ የዴቢ ዋነኛ ተቀናቃኝ እንደሚሆኑም ነው ፍራንስ 24 ያስነበበው።
10 የሀገሪቱ ፖለቲከኞች በፕሬዝዳንታዊ ምርጫው ላይ እንዳይሳተፉ የሀገሪቱ የህገመንግስት ጉዳዮች ምክርቤት መወሰኑ የሚታወስ ነው።
AL-AIN
More Stories
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች
የአራዳ ፓርክ የነዋሪዎችን ሰብአዊ ክብር ያስቀደመ ፕሮጀክት ነው – ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ዶናልድ ትራምፕ በድጋሚ የግድያ ሙከራ ተደረገባቸው