የአሜሪካ ጦር ኢራን በዋሽንግተን ኃይሎች ላይ ለሰነዘረቻቸው የሚሳዔል ጥቃት ሙከራዎች የአጸፋዊ ምላሽ ለመስጠት ሲል፤ ረቡዕ ምሽት ኢራን ላይ ከፍተኛ ድብደባ መፈፀሙን አስታውቋል።
በዚህ ጥቃት “በርካታ” የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ዒላማዎች መመታታቸውን የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (ሴንትኮም) ገልጿል።
ተቀዛቅዞ የነበረው ጥቃት በድጋሚ የተጀመረው፤ ማክሰኞ ዕለት ኢራን በቀጠናው በሚገኙ የአሜሪካ ጦር ሠፈሮች እንዲሁም በሆርሙዝ ወሽመጥ ጉዞ ላይ በነበሩ መርከቦች ላይ ሚሳዔሎችን በማስወንጨፏ እንደሆነ ዕዙ ተናግሯል።
በአሜሪካ ጥቃት የኢራን “ወታደራዊ የዕዝ ማዕከላት፣ የሜሳዔል እና የድሮን ተቋማት፣ የባሕር ዳርቻ ቁጥጥር እና መከላከያ ስፍራዎች፣ እና የባሕር ኃይል አቅሞች” ዒላማ መደረጋቸውም ተገልጿል።
አሜሪካ ለ13 ተከታታይ ቀናት ጥቃት ስትፈጽምበት፤ ኢራንም አጸፋውን ስትመልስበት የቆየው ግጭት ለቀናት አንጻራዊ መረጋጋት ከታየበት በኋላ በድጋሚ ተቀጣጥሏል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ “እጅግ ወዳጅነት የተሞላባቸው ድርድሮች” እየተካሄዱ መሆኑን ተናግረው የነበር ቢሆንም ኢራን በበኩሏንግግር ተጀምሯል መባሉን አስተባብላለች።
More Stories
ከማሻ ደገሌ መንገድ በእጅጉ በመበላሸቱ ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ችግር እንደፈጠረባቸው ነዋሪዎች ቅሬታ አቀረቡ
በአረንጓዴ አሻራ የተተከሉ የአቮካዶ ምርቶች ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ገበያ ተፈላጊ እያደረጓት ነው
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የሥራ ዘመኑን የማጠቃለያ ጉባኤ በታርጫ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል።