ከ20 ዓመት በታች የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በሴቶች 3 ሺ ሜትር መሰናክል ፍጻሜ አልማዝ ዮሀንስ እና ወሰኔ አሰፋ ተከታትለው በመግባት የወርቅ እና የብር ሜዳሊያውን ወስደዋል።
በአሜሪካ እየተደረገ በሚገኘው ውድድር አልማዝ ዮሀንስ የግል ምርጥ ሰዓቷን በማሻሻል ጭምር አሸንፋለች። 9 ደቂቃ 15.81 ርቀቱን ለማጠናቀቅ የወሰደባት ሰዓት ሲሆን በዓመቱ ውስጥ ከተመዘገቡት ፈጣን ሰዓቶችም አንዱ ነው።
2ኛ ደረጃን ይዛ የጨረሰችው አትሌት ወሰኔ አሰፋ 9 ደቂቃ 30.50 በመግባት የዓመቱን ምርጥ ሰዓቷን በማስመዝገብ የብር ሜዳሊያውን ለሀገሯ አስገኝታለች።
More Stories
ኢትዮጵያዊ በዳምጠው ከበደ ተጨማሪ ሜዳሊያ አገኘች
ቴፒ ከተማ እግር ኳስ ክለብ ደማቅ አቀባበል ተደረገለት
የኤሲሚላን የቀድሞ ተጫዋች ፍራንኮ ባሬዚ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ