August 8, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ኢትዮጵያ በአልማዝ ዮሀንስ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳልያ አስመዘገበች

ከ20 ዓመት በታች የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በሴቶች 3 ሺ ሜትር መሰናክል ፍጻሜ አልማዝ ዮሀንስ እና ወሰኔ አሰፋ ተከታትለው በመግባት የወርቅ እና የብር ሜዳሊያውን ወስደዋል።

በአሜሪካ እየተደረገ በሚገኘው ውድድር አልማዝ ዮሀንስ የግል ምርጥ ሰዓቷን በማሻሻል ጭምር አሸንፋለች። 9 ደቂቃ 15.81 ርቀቱን ለማጠናቀቅ የወሰደባት ሰዓት ሲሆን በዓመቱ ውስጥ ከተመዘገቡት ፈጣን ሰዓቶችም አንዱ ነው።

2ኛ ደረጃን ይዛ የጨረሰችው አትሌት ወሰኔ አሰፋ 9 ደቂቃ 30.50 በመግባት የዓመቱን ምርጥ ሰዓቷን በማስመዝገብ የብር ሜዳሊያውን ለሀገሯ አስገኝታለች።