August 4, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ በ190 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገነባው ዘመናዊ መናኸሪያ የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ በአንድነት ቀበሌ በ190ሚሊዮን ብር በላይ በጀት የሚገነባው አዲሱ ዘመናዊ የሕዝብ ትራንስፖርት መናኸሪያ የመሠረት ድንጋይ ተቀምጧል ።

የእንካን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የሸካ ዞን ምክትል አስተዳደርና የውሃ፣ማዕድንና ኢነርጂ መምሪያ ኃላፊ አቶ በላቸው ጋራ በወቅቱ እንደተናገሩት የመናኸሪያ ግንባታው የህብረተሰቡን የረጅም ጊዜ ጥያቄ የሚመልስና ዘመናዊ የትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠት ወሳኝ በመሆኑ ለዚህም የክልሉ መንግስት ለሰጠው ምላሽ አመስግነዋል ።

የክልሉ መንገድ ልማትና ትራንስፓርት ቢሮ ኃላፊ ፋጂኦ ሳፒ አዲሱ መናኸሪያ የቴፒ ከተማን የንግድና የኢኮኖሚ ትስስር የሚያሳድግ ከመሆኑም በላይ በአካባቢው ለረጅም ጊዜ የቆየውን የትራንስፖርት መናኸሪያ እጥረትና መጨናነቅ በዘላቂነት ለመቅረፍ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ገልፀዋል ።

መናኸሪያያው 400 በላይ ተሽከርካሪዎችን ማስተናገድ የሚችልና ግንባታውም በአንድ አመት ጊዜ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆን ተናግረዋል ።

ግንባታው በተቀመጠለት የጥራት ደረጃና የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ የክልሉ መንግሥት የቅርብ ክትትልና ድጋፍ እንደሚያደርግም አረጋግጠዋል።