ሕጉ ከቀጣይ ዓመት ታኅሣሥ ጀምሮ የሚተገበር ሲሆን፤ እርምጃውን በመውሰድ ፈረንሳይ በአውሮፓ የመጀመሪያዋ አገር ትሆናለች።
በሕጉ መሠረት ፈረንሳይ ውስጥ ማኅበራዊ ሚዲያ ለመጠቀም የዕድሜ ማረጋገጫ ማስገባት አስፈላጊ ይሆናል።
ዩናይትድ ኪንግደም እና አውሮፓ ኅብረት የታዳጊዎችን አእምሯዊ ጤና ለመጠበቅ ተመሳሳይ ውሳኔዎች አሳልፈዋል።
የሥልጣን ዘመናቸው እየተገባደደ ያለው የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የሕጉን መጽደቅ እንደሚደግፉ ገልጸዋል።
የሕጉ ተግባራዊነት ላይ ጥያቄ ያነሱ ቢኖሩም የተጠቃሚዎችን ዕድሜ ለማረጋገጥ የተለያዩ መንገዶች ጥቅም ላይ እንደሚውሉ መንግሥት ገልጿል።
ከፊታችን መስከረም ጀምሮ ከ15 ዓመት በታች ያሉ ታዳጊዎች የዕድሜ ማረጋገጫ ሳይሰጡ ማኅበራዊ ሚዲያ ገጽ መክፈት አይችሉም። ከታኅሣሥ በኋላ ደግሞ ሁሉም ፈረንሳውያን ዕድሜያቸው ከ15 ዓመት በላይ መሆኑን የግድ ማረጋገጥ ይጠበቅባቸዋል።
ሕጉ መተግበር ሲጀምር የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾች የፈረንሳይ መንግሥት ያስቀመጠውን የዕድሜ ማረጋገጫ መንገድ መጠቀም ይኖርባቸዋል።
BBC
More Stories
አሜሪካ በኢራን ጦርነት ከ37 ቢሊየን ዶላር በላይ እንዳወጣች ተገለፀ::
የአፍሪካ እና የባህረ ሰላጤው (ገልፍ) የኢኮኖሚያዊ ትብብር መድረክ መካሄድ ጀመረ
የጅማ ዩኒቨርሲቲ የባዮጋዝ የምርምር ማዕከል ለአፈር ለምነትና ለግብርና ምርታማነት አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው