2018 በጀት ዓመት የተቋማት ማጠቃለያ ሪፖርት ግምገማ በማሻ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
አቶ በላቸው ጋራ የሸካ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ በመድረኩ ባደረጉት መክፈቻ ንግግር እንደገለፁት በዞኑ ሴክተር መ/ቤቶች በባለፈው በጀት ዓመት ታቅደው በተከናወኑ ተግባራት መሠረታዊ የህዝብ ጥያቄዎች እየተመለሱ መምጣቱን ገልፀው ከሚጠበቀው አንፃር ግን ብዙ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።
አቶ በላቸው አያይዘውም በግብርና፣ንግድ እና ገበያ ልማት፣ከተማ ልማት፣እና በገቢ አሰባሰብ ተቋማት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በመስራት ወቅታዊ የኑሮ ውድነትን ለመቆጣጠር፣የኮሪደር ልማት ስራን ማፍጠን እና የግብር አሰባሰብ ስርዓቱን ማዘመን እንዲሁም ተቋማት የአፈፃፀማቸውን ደካማና ጠንካራ ጎን በመለየት ቀጣይ የተሻለ ለመስራት መዘጋጀት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
የሸካ ዞን ፕላን እና ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ጸያጻ በለጠ የ2018 በጀት ዓመት የተቋማት ማጠቃለያ ሪፖርት ለተሳታፊዎች እንቀረቡ ይገኛል።
#ዞን መንግስት ኮምኒኬሽን
More Stories
አሜሪካ በኢራን ጦርነት ከ37 ቢሊየን ዶላር በላይ እንዳወጣች ተገለፀ::
ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች ማኅበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ የሚያግደው ሕግ በፈረንሳይ ምክር ቤት ጸደቀ።
የአፍሪካ እና የባህረ ሰላጤው (ገልፍ) የኢኮኖሚያዊ ትብብር መድረክ መካሄድ ጀመረ