ማሻ፤ ግንቦት 16/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) የ2025/26 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የውድድር ዓመት ዛሬ ምሽት 12 ሰዓት በሚደረጉ ጨዋታዎች ፍጻሜውን ያገኛል፡፡
በዛሬ ዕለት ወልቭስ እና በርንሌይን ተከትሎ ወደ ሻምፒዮንሺፕ የሚወርደው ሦስተኛ ቡድን የሚለይባቸው ጨዋታዎች ይጠበቃሉ፡፡
በአሰልጣኝ ሮቤርቶ ዲዘርቢ የሚመራው የሰሜን ለንደኑ ክለብ ቶተንሃም ሆትስፐር በሜዳው ኤቨርተንን ያስተናግዳል፡፡
ከፈረንጆቹ 1977 በኋላ ከእንግሊዝ ዋናው ሊግ የመውረድ ስጋት ያለበት የሰሜን ለንደኑ ክለብ ከጨዋታው አንድ ነጥብ የሚያገኝ ከሆነ በሊጉ መቆየቱን ያረጋግጣል፡፡
ሌላኛው የለንደን ክለብ ዌስትሃም ዩናይትድ ወደ ሻምፒዮንሺፕ የመውረድ ስጋት ያለበት ሲሆን፥ በሜዳው ከሊድስ ዩናይትድ ጋር ይፋለማል፡፡
ዌስትሃም ዩናይትድ በሊጉ ለመቆየት የራሱን ጨዋታ አሸንፎ የቶተንሃም ሆትስፐርን መሸነፍ ይጠብቃል።
More Stories
ኢትዮጵያ ከዓለም ዋንጫው ውጪ ሆነች
ብሩኖ ፈርናንዴዝ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ተብሎ ተመረጠ
ማይክል ካሪክ የማንቸስተር ዩናይትድ ቋሚ አሰልጣኝ ሆኖ ተሾመ