May 22, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ማይክል ካሪክ የማንቸስተር ዩናይትድ ቋሚ አሰልጣኝ ሆኖ ተሾመ


ማይክል ካሪክ የማንችስተር ዩናይትድ ቋሚ አሰልጣኝ ሆኖ ተሹሟል።

ካሪክ ከሩበን አሞሪም ስንበት በኋላ ማንቸስተር ዩናይትድን በመረከብ ቡድኑን ለአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎ አብቅቶታል።

ማንችስተር ዩናይትድ ለማይክል ካሪክ የ2 ዓመት ኮንትራት የሰጠው ሲሆን በሚያስመዘግባቸው ስኬቶች ኮንትራቱ ይራዘማል ተብሏል።

ማይክል ካሪክ በማንቸስተር ዩናይትድ ጊዚያዊ የአሰልጣኝነት ቆይታው አርሰናል ፣ ማንቸስተር ሲቲ ፣ ሊቨርፑል፣ ቶተንሀም እና ቼልሲን በማሸነፍ በሊጉ ወጥ የሆነ ብቃትን ማሳየት ችሏል።