አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ም/ቤት ቋሚ መቀመጫ ለማግኘት የምታነሳው ጥያቄ ፍትሃዊ ነው የአዘርባጃን ፕሬዚዳንት ኢልሃም አሊዬቭ፡፡
4ኛው የሹሻ ዓለም አቀፍ የሚዲያ ፎረም “የመገናኛ ብዙሃን ሚና ሰላምና መተማመንን ለመመለስ” በሚል መሪ ሃሳብ በአዘርባጃን ሹሻ ከተማ መካሄድ ጀምሯል፡፡
ፕሬዚዳንቱ በፎረሙ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፥ የተባበሩት መንግሥታት አካታችና አሳታፊ መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል።
አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ም/ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዲኖራት የምታነሳው ጥያቄ ፍትሃዊና ተገቢ መሆኑን አንስተዋል፡፡
ድምጽን በድምጽ የመሻር መብት ያላቸው ተጨማሪ አካላት በምክር ቤቱ ካልተካተቱ በግጭት አፈታትና በዓለም አቀፍ ግንኙነት ላይ እክል እየፈጠረ ይቀጥላል ነው ያሉት፡፡
አዘርባጃን ከአፍሪካ ሀገራት ጋር ያላት ግንኙነት እየተጠናከረ መምጣቱንም ተናግረዋል፡፡
በፎረሙ ላይ ከ53 ሀገራት የተውጣጡ ከ160 በላይ ተሳታፊዎች፣ 30 የዜና ወኪሎች፣ 60 የሚዲያ ተቋማት እንዲሁም 10 ዓለም አቀፍ የጥናትና ምርምር ተቋማት እየተካፈሉ ይገኛሉ።
ኤፍ ኤም ሲ
More Stories
የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በመከላከያ ጠቅላይ መመሪያ ግቢ የ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በይፋ አሥጀምረዋል።
የክልሉ ወጪዎችን በራስ አቅም ለመሸፈን የሚያስችል የገቢ አሰባሰብ አቅም እየተፈጠረ ነው፦ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)
መሰረታዊና ሀገራዊ ችግሮችን በምክክር መፍታት ለኢትዮጵያ አዲስ ምዕራፍ ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ቃል-አቀባይ አቶ ጥበቡ ታደሰ ገለጹ፡፡