በ2010 በጀት ዓመት የኢትዮጵያ ዓመታዊ የወጪ ንግድ ገቢ 2.66 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር እንደነበረ ያወሳው የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ዘርፉን ለማሳደግ ባለፉት ዓመታት በተደረገ የሪፎርም እርምጃዎች በታሪክ ከፍተኛ የተባለውን የወጪ ንግድ ገቢ ለማስመዝገብ ተችሏል ሲል አስታውቋል።
በዚህም መሠረት በ2018 በጀት ዓመት ከዘርፉ 7.25 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ እንደነበረ የጠቀሰው ሚንስቴር መሥሪያ ቤቱ፣ የበጀት ዓመቱ ሊጠናቀቅ የሁለት ወራት ጊዜ በቀረበት በዚህ ወቅት በ10 ወራት ውስጥ ብቻ ወደ 8.71 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር በመገኘቱ የዕቅዱን 120.17 በመቶ ማሳካት እንደተቻለ ገልጿል።
ይህ ዕድገት ሊመዘገብ የተቻለባቸው ምክንያቶች አንዱ የወጪ ንግድ ምርቶችን ዓይነት ማብዛት በመቻሉ እና በጥራት ረገድ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነታቸውን ለማሳደግ በመሠራቱ እንደኾነ ያመላከተው የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚንስቴር የወጪ ንግድ ምርቶች ጥራትን ለማስጠበቅ በተሠራው ሥራ ጥራታቸውን የጠበቁና ተወዳዳሪነታቸው የላቀ ምርቶችን ማቅረብ በመቻሉ የኢትዮጵያን ምርቶች የሚቀበሉ አዳዲስ የውጭ ሀገራት የገበያ መዳረሻዎችን ቁጥር መጨመሩ ለገቢው ማደግ ዋና ምክንያት ነው ብሏል
ሚንስቴር መሥሪያ ቤቱ ስኬቱ የኢትዮጵያን የውጭ ምንዛሬ እጥረት በዘላቂነት ለመቅረፍና የኢኮኖሚውን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ትልቅ ተስፋ የሰጠ እንደኾነ በወል ትስስር ገጹ ማስፈሩን ትርታ ተመልክቷል።
ዓመታዊ የወጪ ንግድ ያስገኘው ገቢ ጨምሯል ተባለ
More Stories
አዲሱ የማዕድንና ኢንዱስትሪ ትስስር
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአፍሪካ አቪዬሽን ኢንዱስትሪ የጀርባ አጥንት መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ ነው
የሸካ ህዝቦች ልማት ማህበር የጀመረው የሰንበት ገቢያ በበዓል ወቅት ከሚፈጠረው የዋጋ ንረት ታድጎናል ሲሉ የሸካ ዞን ማሻ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ።