ጋዜጠኞች ሙያቸውን እና ሕግን እንዴት መከተል እንዳለባቸው ሊያውቁ ይገባል አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ”የሚዲያ እመርታ ለትርክት ግንባታ” በሚል መሪ ቃል በሚዲያ ዘርፍና ተቋማት ላይ የተመዘገቡ ስኬቶች ላይ የሚመክር መድረክ ተካሂዷል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሚዲያው ዘርፍና ተቋማት ዙሪያ ያላቸውን ሀሳብ ለመድረኩ አጋርተዋል፡፡
በዚህም ከለውጡ ማግስት የመገናኛ ብዙኃን የሀሳብ ነፃነት እንዲከበር እና በሙያቸው ምክንያት የታሰሩ ጋዜጠኞች እንዲፈቱ መደረጉን አስታውሰዋል።
የመገናኛ ብዙኃን ነፃነትን ለማረጋገጥ የተዘጉ ሚዲያዎች እንዲከፈቱ እንዲሁም የተከለከሉ ሚዲያዎች እና ጋዜጠኞች ወደ ሀገር ቤት እንዲገቡ እና አሳሪ ሕጎች እንዲሻሻሉ መደረጉን አውስተዋል፡፡
ነገር ግን የለውጡ መንግሥት በሚዲያው ዘርፍ አበረታች ርምጃዎችን ቢወስድም ጋዜጠኞች ነፃነትን ማስተዳደር ባለመቻላቸው በርካታ ችግሮች ተከስተዋል ነው ያሉት፡፡
ሚዲያው ክፍት እንዲሆን ከተደረገ በኋላ በቀላሉ ወደ ኢንዱስትሪው ለመግባት የተቸገሩ የመገናኛ ብዙኃን እና ጋዜጠኞች አሉ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ÷ ጋዜጠኞች ሙያቸውን እና ሕግን እንዴት መከተል እንዳለባቸው ሊያውቁ ይገባል ብለዋል፡፡
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።