በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ግማሽ ፍጻሜ የመልስ ጨዋታ አርሰናል አትሌቲኮ ማድሪድን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለፍጻሜ ደርሷል፡፡ በኤምሬትስ በተደረገው ጨዋታ ቡካዮ ሳካ የማሸነፊያዋን ግብ አስቆጥሯል፡፡
በመጀመሪያው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ በስፔን አንድ አቻ ተለያይቶ የተመለሰው አርሰናል በድምር ውጤት 2 ለ 1 በማሸነፍ የፍጻሜ ተፋላሚ መሆኑን አረጋግጧል፡፡
በዚህ ዓመት በሻምፒዮንስ ሊግ አንድም ጨዋታ ያልተሸነፈው የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል በአውሮፓ ትልቁ የክለቦች ውድድር ከ20 ዓመት በኋላ የደረሰበትም ምሽት ሆኗል፡፡
አርሰናል በቡዳፔስት በሚደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ከባየር ሙኒክ እና ፒኤስጂ አሸናፊ የሚገናኝም ይሆናል፡፡
More Stories
ኢትዮጵያዊ በዳምጠው ከበደ ተጨማሪ ሜዳሊያ አገኘች
ቴፒ ከተማ እግር ኳስ ክለብ ደማቅ አቀባበል ተደረገለት
የኤሲሚላን የቀድሞ ተጫዋች ፍራንኮ ባሬዚ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ