በ35ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ማንቼስተር ዩናይትድ ሊቨርፑልን 3 ለ 2 አሸንፏል፡፡
11 ሰዓት 30 ላይ በኦልድትራፎርድ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የማንቼስተር ዩናይትድን የማሸነፊያ ግቦች ማቲያስ ኩኛ፣ ቤንያሚን ሼሽኮ እና ኮቢ ማይኖ አስቆጥረዋል፡፡
ሊቨርፑልን ከሽንፈት ያልታደጉ ግቦችን ደግሞ ዶሚኒክ ሶቦዝላይ እና ኮዲ ጋክፖ ከመረብ አሳርፈዋል፡፡
ውጤቱን ተከትሎ ማንቼስተር ዩናይትድ በቀጣይ የውድድር ዓመት የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳታፊ መሆኑን አረጋግጧል፡፡
አስቀድሞ በተደረገ በሌላ የሊጉ መርሐ ግብር ቦርንማውዝ ክሪስታል ፓላስን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
የሊጉ ጨዋታ ሲቀጥል አስቶንቪላ ምሽት 3 ሰዓት ላይ በሜዳው ቪላ ፓርክ ቶተንሃም ሆትስፐርን ያስተናግዳል፡
More Stories
ኬንያዊው አትሌት በሽልማት ተንበሸበሸ
የቀድሞ ብቃቱ ላይ የማይገኘው ቡካዮ ሳካ
የለንደን ማራቶን በታሪክ ግዙፉ የማራቶን ውድድር በመሆን የጊነስ ወርልድ ሪከርድ ተቀዳጀ