April 23, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ማንችስተር ስቲ የሊጉን መሪነት ከአርሰናል ሲረከብ በርንሌይ ወርዷል

በ34ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንችስተር ሲቲ በርንሌይን 1 ለ 0 አሸንፏል። በተርፍ ሙር በተደረው ጨዋታ ሃለንድ የሲቲን የማሸነፊያ ግብ አስቆጥሯል።

ማንችስተር ሲቲ ከነሀሴ ወር በኋላ ለመጀመርያ ጊዜ የፕሪሚየር ሊጉን መሪነት ከአርሰናል ተረክቧል። ሲቲ ከአርሰናል ጋር እኩል 70 ነጥብ እና እኩል የግብ ክፍያ ቢኖራቸውም ብዙ ግብ በማስቆጠር በልጦ ሊጉን መምራት ጀምሯል።

እስካሁን ማንቸስተር ሲቲ ያስቆጠራቸው ግቦች 66 ሲሆኑ፣ አርሰናል ደግሞ 63 ግቦችን አስቆጥሯል።

በርንሌይ ዎልቭስን ተከትሎ ከፕሪሚየር ሊጉ የወረደ 2ኛው ክለብ ሆኗል።