በ34ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንችስተር ሲቲ በርንሌይን 1 ለ 0 አሸንፏል። በተርፍ ሙር በተደረው ጨዋታ ሃለንድ የሲቲን የማሸነፊያ ግብ አስቆጥሯል።
ማንችስተር ሲቲ ከነሀሴ ወር በኋላ ለመጀመርያ ጊዜ የፕሪሚየር ሊጉን መሪነት ከአርሰናል ተረክቧል። ሲቲ ከአርሰናል ጋር እኩል 70 ነጥብ እና እኩል የግብ ክፍያ ቢኖራቸውም ብዙ ግብ በማስቆጠር በልጦ ሊጉን መምራት ጀምሯል።
እስካሁን ማንቸስተር ሲቲ ያስቆጠራቸው ግቦች 66 ሲሆኑ፣ አርሰናል ደግሞ 63 ግቦችን አስቆጥሯል።
በርንሌይ ዎልቭስን ተከትሎ ከፕሪሚየር ሊጉ የወረደ 2ኛው ክለብ ሆኗል።
More Stories
ኢትዮጵያዊ በዳምጠው ከበደ ተጨማሪ ሜዳሊያ አገኘች
ቴፒ ከተማ እግር ኳስ ክለብ ደማቅ አቀባበል ተደረገለት
የኤሲሚላን የቀድሞ ተጫዋች ፍራንኮ ባሬዚ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ