April 25, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ቡካዮ ሳካ ለነገው ጨዋታ ይደርሳል፡- ሚኬል አርቴታ

አርሰናል በ34ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ነገ በሜዳው ከኒውካስትል በሚያርገው ጨዋታ ጉዳት ላይ የነበረው ቡካዮ ሳካ እንደሚደርስ ሚኬል አርቴታ ተናግሯል፡፡

የእንግሊዛዊው ተጫዋች መመለስ ለቡድኑ ወደ አሸናፊነት መመለስ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረውም ስፔናዊው ሰው ገልጿል፡፡

በተመሳሳይ ዩሪየን ቲምበርም ወደ ቡድኑ የተመለሰ ተጫዋች ሲሆን ሪካርዶ ካላፊዮሪም ለጨዋታው ዝግጁ መሆኑን አሰልጣኙ ተናግሯል፡፡

ባለፉት ሁለት ተከታታይ የሊግ ጨዋታዎች የተሸነፉት መድፈኞቹ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ የሚያደርጉት ጨዋታ ምሽት 1 ሰዓት ከ 30 ላይ በኤምሬትስ የሚጀመር ይሆናል፡፡