April 16, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

አሜሪካዊቷ የኦሊምፒክ ሻምፒዮን አዲስ አበባ ገባች!

ከዓለማችን የአጭር ርቀት ሩጫ ኮከቦች መካከል አንዷ የሆነችው አሜሪካዊቷ የሶስት ኦሎምፒክ ወርቅ ሜዳሊያዎች ባለቤት ጋብሪኤል ቶማስ (ጋቢ) ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ በምታስተናግደው ግራንድ ፕሪ ውድድር ለመሳተፍ አዲስአበባ ገባች።

በፓሪስ ኢሊምፒክ የደመቀችው ጋቢ ቶማስ አዲስ አበባ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ስትደርስ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን ፕሬዝደንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህንን ጨምሮ የፌደሬሽኑ የስራ ሃላፊዎች አቀባበል አድርገውላታል።