ማሻ፤ ሚያዝያ 6/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) በ32ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሊድስ ዩናይትድ ማንቼስተር ዩናይትድን 2 ለ 1 አሸንፏል።
ምሽት 4 ሰዓት ላይ በኦልድትራፎርድ በተካሄደው ጨዋታ የሊድስ ዩናይትድን ሁለቱንም የማሸነፊያ ግቦች ኦካፎር አስቆጥሯል።
ማንቼስተር ዩናይትድን ከሽንፈት ያልታደገችዋን ብቸኛ ግብ ደግሞ ካስሚሮ ከመረብ አሳርፏል።
በጨዋታው የማንቼስተር ዩናይትድ የተከላካይ ስፍራ ተጫዋች ሊሳንድሮ ማርቲኔዝ በቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥቷል።
More Stories
ሪያል ማድሪድ የዓለማችን ውዱ ክለብ ሆነ
ፒኤስጂ በተከታታይ ለ2ኛ ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን አሸነፈ
ክሪስታል ፓላስ የአውሮፓ ኮንፍረንስ ሊግ ሻምፒዮን ሆነ!