በማስጀመሪያ መረሃ ግብር ላይ የተገኙት የሸካ ዞን ሴቶች ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ አካልነሽ አየነው የነገ ሀገር ተረካቢ ትውልድ ጤንነቱ የተገጠበቀ እንዲሆን ክትባቶችን ወቅቱ ተደራሽ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ገልፀው ወላጆችም ልጆቻቸውን እንዲያስከትቡ ጥሪ በማቅረብ ለ5 ዙር የተቀናጀ ክትባት በቴፒ አል ፋሊህ አካዳሚ አስጀምረዋል ።
የቴፒ ከተማ ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ ተሻገር በቀለ በአፍ ጠብታ ለ5ዙር ክትባት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከትምህርት ቤት በተጨማሪ ቤት ለቤት ተደራሽ እንደሚሆን የጠቀሙት ኃላፊው በመደበኛ ክትባት መርሃግብር ተደራሽ ያልሆኑ ወይም መጀምረው ያቋረጡ እድሜያቸው ከ5 አመት በታች የሆኑ ህፃናትን የመለየትና የመከተብ አገልግሎት እንደሚሰጥ ተናግረዋል። ።
በተጓዳኝ የእናቶች ማህፀን ውልቃት(ፈሲቱላ)፣ቆልማማ እግር፣የከንፈር መሰንጠቅ ፣የሥርዓተ ምግብ ችግር ያለባቸውን ህፃናት የመለየትና የህክምና ስራ በተጓዳኝ እንደሚካሄድ ከመረሃ ግብሩ ለማውቅ ተችላል ።።
ከመጋቢት 18 እስከ 21 ድረስ 5ተኛ ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት እንደሚካሄድ ታውቋል።
More Stories
ለወረርሽኝና ለድንገተኛ አደጋ የማይበገር የጤና ስርዓት ለመዘርጋት የጤና ዘርፍ አገልግሎትና አስተዳደር ማሻሻያ ሪፎርምን በሙሉ አቅም ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ የክልሉ ጤና ቢሮ ገለፀ።
የሙዝ የጤና ጥቅሞች 🤍
ከ90 በላይ ኩባንያዎች የሚሳተፉበት ዓለም አቀፍ አውደርዕይ ሊካሄድ ነው