የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ትምህርት ቢሮ የትምህርት አስተዳደር መረጃ ስረዓት ዲጂታላይዘሽን ላይ ያተኮረ የግምገማ መድረክ እየተካሄደ ነዉ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ትምህርት ቢሮ ምክትል የቢሮ ኃላፊና የመማር ማስተማርና ምዘና ዘርፍ ኃላፊ ደስታ ገነሜ(ዶ/ር) ጥራት ያለዉ መረጃ ስረዓት በትምህርት ስረዓቱ ላይ ያለዉን ጉድለት ለመሙላት ጉልህ ሚና እንዳለው ተናግረዋል ።
የትምህርት ጥራት አመላካች ከሆኑ ተግባራት መካከል አንዱ የትምህርት መረጃ ስረዓት መሆኑን ገልፀዉ በየደረጃው ያሉት አካላት የትምህርት መረጃ በጥራት መሙላት እንዳለባቸው አሳስበዋል ።
በባለፉት ግዜያት በማኑዋል ስሰራ የነበረዉ የመረጃ ስረዓት ኦንላይን መደረጉን ተናግረው ይህም ጥራት ያለዉን የትምህርት መረጃ ለማደረጀት አይነተኛ ሚና እንደሚወጣ ገልፀዉ ለዚህም ርዕሰ መምህራን ድርሻቸዉ መወጣት ይገባቸዋል ብለዋል።
የመምህራን ፣የተማርዎች ፣የትምህረት ቤቶች መረጃና የጎልማሶች መሰረታዊ ትምህርት መረጃ በትክክል ከመመዝገብ አንፃር የሚታዩ ክፍተቶች ማረም እንደሚገባ ገልጸዋል ።
በመድረኩ የቢሮዉ የትምህርት አመራር መረጃ ስረዓት ቡድን አቶ ታጠቅ ታደሰ በኩል ሰነድ እየቀረበ ይገኛል።
ጥራት ያለዉ መረጃ ስረዓት በትምህርት ስረዓቱ ላይ ያለዉን ጉድለት ለመሙላት ጉልህ ሚና እንዳለው ተገለፀ
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች