March 19, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

በዞኑ በ2018 በጀት ዓ.ም 6ወራት ውስጥ ለ58ሺ 8መቶ 39 የወባ ታማሚዎች የህክምና አገልግሎት መሰጠት መቻሉ ተገለፀ ።

የሸካ ዞን ምክር ቤት እያካሄደ ባለው 5ኛ ዙር፣ 13ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 24ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ በጤናው ዘርፍ የተከናወኑ ሪፖርት ለምክር ቤቱ ቀርቧል ።

በጉባኤው ላይ የአስፈጻሚ አካላትን የ2018 ዓ.ም የ6 ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ በዞኑ ለጤና ስጋት ከሆኑ በሽታዎች መካከል የወባ በሽታ ወረርሽኝ አንዱ እንደሆነ ተመላክቷል  ።

በዚህም በ2018 በጀት ዓ.ም 6ወራት ውስጥ 58ሺ 8መቶ 39 ሰዎች የወባ በሽታ ተገኝቶባቸው የህክምና አገልግሎት መሰጠት መቻሉን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ ገልፀዋል ።

የበሽታውን ስርጭት ለመከላከል ከጤና ሚናስቴር የቀረቡ 21 ሺ 8መቶ አጎበሮችን ለ9ሺ 99 አባወራዎች እና እማወራዎች ማሰራጨት መቻሉን ዋና አስተዳሪው ጠቁመዋል ።

በሽታውን ለመከላከል ክትባት የመስጠት እና የኬሚካል ርጭት ስራዎች በስፋት በመሰራታቸው የስርጭት መጠኑ እየቀነሰ እንደሚገኝ የተገለፀ ሲሆን ህብረተሰቡም የድርሻውን እንዲወጣ ጠይቀዋል።

የጤና መድህን ስራን በተመለከተ 34 ሺ 55 የመዐጤመ አባል አባወራ እና እማወራ ውስጥ 92 ሺ 65 አባላት በድግግሞሽ የህክምና አገልግሎት እንዳገኙ ተገልጿል ።