March 19, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

የቴፒ ከተማ አስተዳደር 1447ኛውን የዒድ አልፈጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ  ለ80 አቅመ ደካማ ወገኖች የበዓል መዋያ ድጋፍ አደረገ ።



‎ማሻ፤ መጋቢት 10/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) የቴፒ ከተማ አስተዳደር 1447ኛውን የዒድ አልፈጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ  ለ80 አቅመ ደካማ ሙስሊም ወገኖች  160 ሺ ብር  የሚያወጣ የምግብ ዘይትና የዱቄት ድጋፍ  አድርጓል ።

‎የቴፒ ከተማ አስተዳደር  ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አብርሀም ወንድማገኝ እንደገለፁት  ከዚህ ቀደም እንደሚደረገው ሁሉ ከማህረሰቡ ውስጥ አቅመ ደካማ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን በመለየት ከተማ አስተዳደሩ ካለው ነገር  ላይ በየዓመቱ ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ገልፀዋል።

‎አክለውም  አቅመ ደካሞችን መርዳት ከሁሉም ህብረተሰብ የሚጠበቅ ተግባርና ባህል ልናደርገው የሚገባ መሆኑን ገልፀዋል።

‎ የከተማ አስተዳደሩ በየጊዜው እንደሚያደርገው ሁሉ የ1447ኛውን የኢድ አልፈጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ  80 ለሚሆኑ አቅመ ደካማ የህብረተሰብ ክፍሎች 160 ሺህ ብር የሚያወጣ የምግብ ዘይትና የፉርኖ ዱቄት ድጋፍ ማድረጉን አክለዋል ።

‎ድጋፉ ቀጣይነት እንደሚኖረውና ከተማ አስተዳደሩ  በዘላቂነት አቅመ ደካሞችን ከተረጂነት እንዲወጡ ለማድረግ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በትኩረት  እንደሚሰራ ተናግረዋል።

‎በመጨረሻም የቴፒ ከተማ ሴቶች፣ ህፃናት፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ አለምገና አሰፋ በፕሮግራሙ ላይ እንደገለፁት በየአካባቢያችን የተቸገሩ ወገኖችን በበዓላት ወቅት ብቻ ሳይሆን ሁሌም በችግራቸው ጊዜ ከጎናቸው በመሆን እገዛ ማድረግ እንደሚገባ ገልፀዋል ። ዘገባው የቴፒ ከተማ መ/ኮ/ጉ/ ነው።