ማሻ፤ መጋቢት 10/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) የቴፒ ከተማ አስተዳደር 1447ኛውን የዒድ አልፈጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ ለ80 አቅመ ደካማ ሙስሊም ወገኖች 160 ሺ ብር የሚያወጣ የምግብ ዘይትና የዱቄት ድጋፍ አድርጓል ።
የቴፒ ከተማ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አብርሀም ወንድማገኝ እንደገለፁት ከዚህ ቀደም እንደሚደረገው ሁሉ ከማህረሰቡ ውስጥ አቅመ ደካማ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን በመለየት ከተማ አስተዳደሩ ካለው ነገር ላይ በየዓመቱ ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ገልፀዋል።
አክለውም አቅመ ደካሞችን መርዳት ከሁሉም ህብረተሰብ የሚጠበቅ ተግባርና ባህል ልናደርገው የሚገባ መሆኑን ገልፀዋል።
የከተማ አስተዳደሩ በየጊዜው እንደሚያደርገው ሁሉ የ1447ኛውን የኢድ አልፈጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ 80 ለሚሆኑ አቅመ ደካማ የህብረተሰብ ክፍሎች 160 ሺህ ብር የሚያወጣ የምግብ ዘይትና የፉርኖ ዱቄት ድጋፍ ማድረጉን አክለዋል ።
ድጋፉ ቀጣይነት እንደሚኖረውና ከተማ አስተዳደሩ በዘላቂነት አቅመ ደካሞችን ከተረጂነት እንዲወጡ ለማድረግ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል።
በመጨረሻም የቴፒ ከተማ ሴቶች፣ ህፃናት፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ አለምገና አሰፋ በፕሮግራሙ ላይ እንደገለፁት በየአካባቢያችን የተቸገሩ ወገኖችን በበዓላት ወቅት ብቻ ሳይሆን ሁሌም በችግራቸው ጊዜ ከጎናቸው በመሆን እገዛ ማድረግ እንደሚገባ ገልፀዋል ። ዘገባው የቴፒ ከተማ መ/ኮ/ጉ/ ነው።
የቴፒ ከተማ አስተዳደር 1447ኛውን የዒድ አልፈጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ ለ80 አቅመ ደካማ ወገኖች የበዓል መዋያ ድጋፍ አደረገ ።
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።