March 16, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ተማሪዎች በተማሩት ልክ እንዲለኩ ከኩረጃ  የፀዳና የዘመነ  የፈተና አስተዳደር ስርዓትን እውን ማድረግ ያስፈልጋል:-ዶ/ር ደስታ ገነሜ



‎የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ትምህርት ቢሮ  የ2018 ዓመተ ምህረት የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ዙሪያ ዉጤታማ የፈተና አስተዳደር ስርዓት እንዲኖር ያለመ መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነዉ።

‎በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት  የቢሮው ምክትልና የመማር ማስተማርና ምዘና ዘርፍ ኃላፊ ደስታ ገነሜ (ዶ/ር)  የፈተና አስተዳደር ስርዓቱን  ለማዘመን በባለፉት  ጊዜያት በተሰሩት ስራዎች  መሻሻሎች መታየታቸውን ገልፀዋል።

‎በ2017 ትምህርት ዘመን  በፈተና አስተዳደር  የነበሩ ችግሮች በመገምገም በዘንድሮ  ዓመት የተሻለ የፈተና አስተዳር ስርዓት እውን እንዲሆን የባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል ።

‎ተማሪዎች በተማሩት ልክ እንዲለኩ ከኩረጃ  የፀዳና የዘመነ  የፈተና አስተዳደር ስርዓት ድርሻዉ የጎላ መሆኑን ተናግረዋል ።

‎የምዝገባ ሂደት በጊዜ ያለማስከድ ፤በትክክል ያለመመዝገብ እና መሰል ችግሮች በባለፈው ዓመት ፈተና አስተዳደሩ የጋጠሙ ችግሮች መሆናቸዉን ተናግረዉ  በዘንድሮ ዓመት በፈተና ስረዓቱ ችግሮች እንዳይከሰቱ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

‎በትምህርት ስርዓቱ ያለዉን ጉድለት ለመሙላት  የፈተና አስተዳደር ስረዓትን ማዘመን ቁልፍ ተግባር መሆኑን የተናገሩት ዶክተር ደስታ ገነሜ ለዚህም በቴክኖሎጂ የተጋዘ የፈተና አስተዳደር ስርዓት መዘርጋቱን ገልፀዋል።