ማሻ፤ መጋቢት 8/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) ምክር ቤቱ 4ኛ ዓመት 6ኛ መደበኛ ጉባኤውን በዞኑ ቴፒ ከተማ ላይ እንደሚያካሄድ የምክር ቤቱ ዋና አፈጉባኤ አቶ ጌታቸው ኬኒ ገልፀዋል።
በክልሉ በ2018 በጀት ዓመት ስድስት ወራት ፀጥታን የማስጠበቅ ፣ የዝርፊያና የስርቆት ወንጀሎችን መከላከል እንዲሁም ከወሰን ጉዳዮች ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዲፈቱ የማድረግ ስራዎች ላይ ምክር ቤቱ በትኩረት ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል።
ነገ በሚካሄደው በዚህ ጉባኤ ላይ በ2018 ዓ.ም 6 ወራት ውስጥ የተከናወኑ ተግባራት ሪፓርት ቀርቦ ውይይቶች እንደሚደረጉ ዋና አፈጉባኤው በመግለጫቸው ጠቁመዋል ።
በጉባኤው ላይ የክልሉ መንግሥት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ፣ የሁሉም ብሔረሰብ ተወካዮች እና የተለያዩ ተጋባዥ እንግዶች ይሳተፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም ምክር ቤቱ አስታውቋል።
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።