ማሻ፤ ጥር 12/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8)በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የ7ኛ ዙር መርሐ ግብር ከሜዳው ውጭ የኖርዌዩን ቦዶ ግሊምት የገጠመው ማንቼስተር ሲቲ 3 ለ 1 ተሸንፏል፡፡
ካስፐር ሆግ (2) እንዲሁም ጄንስ ሀውጅ ባስቆጠሯቸው ግቦች በቦዶ ግሊምት 3 ለ 0 ሲመሩ የቆዩት ሲቲዎች በባዶ ከመሸነፍ የዳኑበትን ብቸኛ ግብ ራያን ሼርኪ ከመረብ አሳርፏል፡፡
በማንቼስተር ሲቲ በኩል አማካዩ ሮድሪ በሁለት ቢጫ ካርድ 62ኛው ደቂቃ ላይ ከሜዳ ተሰናብቷል።
ቀደም ብሎ ምሽት 12 ሰዓት ከ30 በተደረገው የዕለቱ የመጀመሪያ መርሐ ግብር ክለብ ብሩጅ ካይራት አልማቲን 4 ለ 1 አሸንፏል፡፡
የሻምፒየንስ ሊጉ የ7ኛ ዙር መርሐ ግብር ቀጥለው ሲደረጉ በመድረኩ በዚህ የውድድር ዓመት በብቸኝነት ሁሉንም ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው አርሰናል ምሽት 5 ሰዓት ኢንተር ሚላንን ይገጥማል።
ሪያል ማድሪድ ከሞናኮ፣ ስፖርቲንግ ሊዝበን ከፒኤስጂ፣ ቶተንሃም ሆትስፐር ከቦሩሺያ ዶርትመንድ፣ ቪያሪያል ከአያክስ አምስተርዳም እንዲሁም ኦሎምፒያኮስ ከባየር ሊቨርኩሰን በተመሳሳይ 5 ሰዓት ላይ የሚደረጉ ጨዋታዎች ናቸው።
More Stories
የሸካ ዞን የታዳጊ ወጣቶች የእግርኳስ ቡድን የ2018 ክልል አቀፍ ውድድር የዋንጫ አሸናፊ ሆነ።
5ተኛው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የባህል ስፖርቶች ውድድር፣ የባህል ፌስቲቫል እና የታዳጊ ወጣቶች ምዘና ውድድር የታለመውን ግብ ያሳካ መሆኑ ተገለጸ።
ባካሪ ሳኛ ኢትዮጵያ ገባ