ማሻ፤ ጥር 12/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የ7ኛ ዙር መርሐ ግብር ዛሬ ምሽት ዘጠኝ ጨዋታዎች ተደርገዋል።
በሻምፒየንስ ሊጉ በዚህ የውድድር ዓመት በብቸኝነት ሁሉንም ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው አርሰናል ወደ ጣሊያን አቅንቶ ምሽት 5 ሰዓት ኢንተር ሚላንን ገጥሟል።
በዚህም ኢንተር ሚላንን 3 ለ 1 በመርታት በሻምፒየንስ ሊጉ የአሸናፊነት ጉዞውን አስቀጥሏል።
በሌሎች የሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታዎች ሪያል ማድሪድ ሞናኮን 6 ለ 1 ፣ ስፖርቲንግ ሊዝበን ፒኤስጂን 2 ለ 1፣ ቶተንሃም ሆትስፐር ቦሩሺያ ዶርትመንድን 2 ለ 0፣ አያክስ አምስተርዳም ከሜዳው ውጪ ቪያሪያልን 2 ለ 1 እንዲሁም ኦሎምፒያኮስ ባየር ሊቨርኩሰንን 2 ለ 0 አሸንፈዋል።
ኮፐንሀገን እና ናፖሊ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል።
ቀደም ሲል ምሽት 2 ሰዓት ከ45 በተደረገ ጨዋታ ወደ ኖርዌይ ያቀናው ማንቼስተር ሲቲ በቦዶ ግሊምት 3 ለ 1 የተሸነፈ ሲሆን፤ ቀደም ብሎ ምሽት 12 ሰዓት ከ30 በተደረገው የዕለቱ የመጀመሪያ መርሐ ግብር ክለብ ብሩጅ ካይራት አልማቲን 4 ለ 1 ማሸነፉ ይታወቃል፡፡
More Stories
የሸካ ዞን የታዳጊ ወጣቶች የእግርኳስ ቡድን የ2018 ክልል አቀፍ ውድድር የዋንጫ አሸናፊ ሆነ።
5ተኛው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የባህል ስፖርቶች ውድድር፣ የባህል ፌስቲቫል እና የታዳጊ ወጣቶች ምዘና ውድድር የታለመውን ግብ ያሳካ መሆኑ ተገለጸ።
ባካሪ ሳኛ ኢትዮጵያ ገባ