February 4, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

በአፍሪካ ዋንጫ የደረጃ ጨዋታ ናይጄሪያ ግብጽን በማሸነፍ የነሐስ ሜዳልያ አገኘች

ማሻ፤ ጥር 09/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ናይጄሪያ ግብጽን በማሸነፍ 3ኛውን ደረጃ ይዛ አጠናቀቀች።

ዛሬ ምሽት 1 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ መደበኛ የጨዋታ ጊዜ አልቆ በመለያ ምት ናይጄሪያ ግብጽን 4 ለ 2 በሆነ ውጤት አሸንፋለች፡፡

ይህንን ውጤት ተከትሎም ናይጄሪያ በውድድሩ 3ኛ ደረጃ ይዛ ስታጠናቅቅ ግብጽ 4ኛ ደረጃን ይዛ ጨርሳለች።

የአፍሪካ ዋንጫ በነገው ዕለት ፍጻሜውን የሚያገኝ ሲሆን፥ አዘጋጇ ሀገር ሞሮኮ ከሴኔጋል ጋር ለዋንጫው ይፋለማሉ።