ማሻ፣ ጥር 06/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍኤም 103.8) የብልጽግና ፓርቲ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት የፓርቲ ስራዎች አፈጻጸም የግምገማ መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው።
በመድረኩ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንትና የፓርቲው ዋና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ እና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰውን (ዶ/ር) ከሁሉም ክልሎች እና ከሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ የፓርቲ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
በአቶ አደም ፋራህ የተመራ የአመራሮች ቡድን ሆሳዕና ከተማ ከሚካሄደው የፓርቲው የስድስት ወራት አፈጻጸም ግምገማ መድረክ አስቀድሞ በትናንትናው ዕለት በክልሉ ምስራቅ ጉራጌ እና ስልጤ ዞኖች የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝቷል፡፡
በዚህም አመራሮቹ በቡታጅራ ከተማ የአቮካዶ ዝርያ ማሻሻያ ማዕከል፣ የወንዝ ዳር ፕሮጀክት፣ ቀሸት ንብ ማነብ ስራ ማህበር እና ደስታ ጋርመንትን ምልከታ አድርገዋል።
እንዲሁም በወራቤ ከተማ በመንግሥትና በባለሀብቶች ቅንጅት በ1 ሺህ ሄክታር ላይ በፍጥነት እየለማ የሚገኘውን የሶጃት (ንጋት) የኢንዱስትሪ ማዕከል ያለበትን ደረጃ መመልከታቸው ይታወሳል ሲል ኤፍ ኤም ሲ ዘግቧል
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።