ማሻ፣ ጥር 03/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍኤም 103.8) አሜሪካ በሶሪያ በሚገኘው እስላማዊ መንግስት ብላ በምትጠራው ላይ ከባድ ጥቃት ፈፀመች ተባለ።
ጥቃቱ የተፈጸመው ባለፈው ወር በሶሪያ ፓልሜራ በአሜሪካ ወታደሮች ላይ ለደረሰው ጉዳት የበቀል ምላሽ ነው ስትል ዋሽንግተን አስታውቃለች።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ እንዳስታወቀው ፣ አይ አይ ኤስ ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት አድርሷል።
ዘመቻ ሀውክአይ በተሰኘው ትራምፕ መራሽ ጥቃት አይ ኤስ ሲጠቀምበት የነበረው የጦር መሳሪያ መውደሙን ማዕከላዊ ዕዙ አክሎ ገልጿል።
አይ ኤስ ላይ የተወሰደው እርምጃ ለወደፊቱ ቡድኑ ለሚያደርገው ጥቃት ከባድ አጸፋ እንደሚጠብቀው ለማስጠንቀቅ ነው ሲሉ የዋሽንግተን ባለስልጣናት ተናግረዋል።
በአሜሪካ ጦር እና ተባባሪዎች ላይ የሚደርስ ጥቃት መልሱ የከፋ መሆኑን አይ ኤስ እና ሌሎች ቡድኖች ማወቅ አለባቸው ሲል ማዕከላዊ ዕዙ በኤክስ ገፁ ላይም አስፍራሯል ሲል ታይምስ ኦፍ ኢንዲያን ጠቅሶ ኤን ቢሲ ኢትዮጵያ ዘግቧል።
More Stories
ሮቦቶችም ተማሪ ሆኑ! በቻይና የተከፈተው የዓለማችን መጀመሪያው የሮቦቶች ትምህርት ቤት አስገራሚ እውነታ
የግል ጄታቸውን ለሕዝብ አምቡላንስ አገልግሎት የለገሱት ጋናዊው ቱጃር
ፌራሪ የመጀመሪያውን ባለ 5 መቀመጫ የኤሌክትሪክ መኪና አስተዋወቀ