ማሻ፣ ጥር 01/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍኤም 103.8) በጥቃቱ አውዳሚ ነው የሚባለው ኦሬሽኒክ ሚሳኤል ጥቅም ላይ የዋለ ሲሆን፥ የዩክሬን ቁልፍ ወታደራዊና መሰረተ ልማት ተቋማት ላይ ያነጣጠረ እንደነበር ሬውተርስ አስነብቧል።
በዚህም በፑቲን ላይ ተፈጽሟል ለተባለው ጥቃት ጥቅም ላይ የሚውሉ ድሮን ማምረቻዎች እና የዩክሬን ወታደራዊ ተቋማት እንዲሁም የሃይል መሰረተ ልማቶች ኢላማ ተደርገዋል ነው የተባለው።
የኒውክሌር አረር መሸከም ይችላል የሚባለው ይህ ሚሳኤል ካለው ፍጥነት አንጻር ከተተኮሰ በኋላ ማምከን አስቸጋሪ መሆኑን ዘገባው አስታውሷል።
የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴርም በጥቃቱ በርካታ ድሮኖችን እና ከፍተኛ አቅም ያላቸውን የጦር መሳሪያዎች ማውደሙን ነው የገለጸው።
ባለፈው ታኅሣሥ ወር በፑቲን ላይ ተፈጽሟል ያለውን ጥቃት “የሽብር ድርጊት” ያለው ሚኒስቴሩ፥ ዩክሬን ለምትፈጽመው ጥቃት ከባድ አፀፋዊ ምላሽ ታገኛለች ሲልም አስጠንቅቋል።
ሬውተርስ
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች