ማሻ፣ ጥር 01/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍኤም 103.8) ባለፈው ረቡዕ በስኮትላንድ ሰሜናዊ ምስራቅ ዓለም አቀፍ የባህር ጠረፍ የተያዘችው መርከብ ‘ማሪኔራ’ ተብላ የምትጠራ ሲሆን፥ ማዕቀብ የተጣለበትን የቬኒዝዌላ የነዳጅ ዘይት የጫነች ናት በሚል በአሜሪካ የአውሮፓ ዕዝ ጦር መያዟ ይታወሳል።
28 አባላት ያሏት መርከቧ ሁለቱ ሩሲያውያን ሲሆኑ፥ 17 ዩክሬናውያን፣ 3 የጆርጂያ እና 3 የህንድ ዜጎች ይገኙበታል።
የሩሲያ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤትም የትራምፕ አስተዳደር ዜጎቹን ስለለቀቀለት ምስጋናውን አቅርቧል።
ሚኒስቴሩ በትናንትናው ዕለት የመርከቧ መያዝ አግባብነት የሌለውና በአካባቢው ዳግም ውጥረትን የሚያነግስ ነው ሲል ማስጠንቀቁን አር ቲ በዘገባው አስታውሷል።
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።