ማሻ፣ ጥር 01/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍኤም 103.8) ባለፈው ረቡዕ በስኮትላንድ ሰሜናዊ ምስራቅ ዓለም አቀፍ የባህር ጠረፍ የተያዘችው መርከብ ‘ማሪኔራ’ ተብላ የምትጠራ ሲሆን፥ ማዕቀብ የተጣለበትን የቬኒዝዌላ የነዳጅ ዘይት የጫነች ናት በሚል በአሜሪካ የአውሮፓ ዕዝ ጦር መያዟ ይታወሳል።
28 አባላት ያሏት መርከቧ ሁለቱ ሩሲያውያን ሲሆኑ፥ 17 ዩክሬናውያን፣ 3 የጆርጂያ እና 3 የህንድ ዜጎች ይገኙበታል።
የሩሲያ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤትም የትራምፕ አስተዳደር ዜጎቹን ስለለቀቀለት ምስጋናውን አቅርቧል።
ሚኒስቴሩ በትናንትናው ዕለት የመርከቧ መያዝ አግባብነት የሌለውና በአካባቢው ዳግም ውጥረትን የሚያነግስ ነው ሲል ማስጠንቀቁን አር ቲ በዘገባው አስታውሷል።
More Stories
ሮቦቶችም ተማሪ ሆኑ! በቻይና የተከፈተው የዓለማችን መጀመሪያው የሮቦቶች ትምህርት ቤት አስገራሚ እውነታ
የግል ጄታቸውን ለሕዝብ አምቡላንስ አገልግሎት የለገሱት ጋናዊው ቱጃር
ፌራሪ የመጀመሪያውን ባለ 5 መቀመጫ የኤሌክትሪክ መኪና አስተዋወቀ