February 4, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

አሜሪካ ከቀናት በፊት ከያዘቻትና የሩሲያ ሰንደቅ አላማ ከምታውለበልብ የንግድ መርከብ ውስጥ ሁለት ሩሲያውያንን መልቀቋን የሩሲያ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አስታውቋል።

ማሻ፣ ጥር 01/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍኤም 103.8) ባለፈው ረቡዕ በስኮትላንድ ሰሜናዊ ምስራቅ ዓለም አቀፍ የባህር ጠረፍ የተያዘችው መርከብ ‘ማሪኔራ’ ተብላ የምትጠራ ሲሆን፥ ማዕቀብ የተጣለበትን የቬኒዝዌላ የነዳጅ ዘይት የጫነች ናት በሚል በአሜሪካ የአውሮፓ ዕዝ ጦር መያዟ ይታወሳል።

28 አባላት ያሏት መርከቧ ሁለቱ ሩሲያውያን ሲሆኑ፥ 17 ዩክሬናውያን፣ 3 የጆርጂያ እና 3 የህንድ ዜጎች ይገኙበታል።

የሩሲያ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤትም የትራምፕ አስተዳደር ዜጎቹን ስለለቀቀለት ምስጋናውን አቅርቧል።

ሚኒስቴሩ በትናንትናው ዕለት የመርከቧ መያዝ አግባብነት የሌለውና በአካባቢው ዳግም ውጥረትን የሚያነግስ ነው ሲል ማስጠንቀቁን አር ቲ በዘገባው አስታውሷል።