ማሻ፣ ጥር 01/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍኤም 103.8) ባለፈው ረቡዕ በስኮትላንድ ሰሜናዊ ምስራቅ ዓለም አቀፍ የባህር ጠረፍ የተያዘችው መርከብ ‘ማሪኔራ’ ተብላ የምትጠራ ሲሆን፥ ማዕቀብ የተጣለበትን የቬኒዝዌላ የነዳጅ ዘይት የጫነች ናት በሚል በአሜሪካ የአውሮፓ ዕዝ ጦር መያዟ ይታወሳል።
28 አባላት ያሏት መርከቧ ሁለቱ ሩሲያውያን ሲሆኑ፥ 17 ዩክሬናውያን፣ 3 የጆርጂያ እና 3 የህንድ ዜጎች ይገኙበታል።
የሩሲያ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤትም የትራምፕ አስተዳደር ዜጎቹን ስለለቀቀለት ምስጋናውን አቅርቧል።
ሚኒስቴሩ በትናንትናው ዕለት የመርከቧ መያዝ አግባብነት የሌለውና በአካባቢው ዳግም ውጥረትን የሚያነግስ ነው ሲል ማስጠንቀቁን አር ቲ በዘገባው አስታውሷል።
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።