ማሻ፣ ታህሳስ 26/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍኤም 103.8) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 20ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ወልቭስ ዌስትሃም ዩናይትድን 3 ለ 0 በማሸነፍ በሊጉ የመጀመሪያ ድሉን አስመዝግቧል።
ምሽት 12 ሰዓት ላይ በሜዳው ዌስትሃም ዩናይትድን ያስተናገደው ወልቭስ አሪያስ፣ ዋንግ ሂ-ቻን (በፍጹም ቅጣት ምት) እና ማኔ ባስቆጠሯቸው ግቦች ሶስት ነጥብ ይዞ ወጥቷል።
ባለፈው ሳምንት ወደ ኦልድ ትራፎርድ አቅንቶ ከማንቼስተር ዩናይትድ ጋር ነጥብ ተጋርቶ የተመለሰው ወልቭስ ዛሬ ባደረገው ጨዋታ በውድድር ዘመኑ በሊጉ ለመጀመሪያ ጊዜ ለማሸነፍ በቅቷል።
በሊጉ ግርጌ ላይ የሚገኘው ወልቭስ ነጥቡን 6 አድርሷል።
በተመሳሳይ ሰዓት በተደረገ ጨዋታ ብራይተን በርንሌይን 2 ለ 0 አሸንፏል።
More Stories
የሸካ ዞን የታዳጊ ወጣቶች የእግርኳስ ቡድን የ2018 ክልል አቀፍ ውድድር የዋንጫ አሸናፊ ሆነ።
5ተኛው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የባህል ስፖርቶች ውድድር፣ የባህል ፌስቲቫል እና የታዳጊ ወጣቶች ምዘና ውድድር የታለመውን ግብ ያሳካ መሆኑ ተገለጸ።
ባካሪ ሳኛ ኢትዮጵያ ገባ