February 4, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ሴኔጋል ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቀለች

ማሻ፣ ታህሳስ 25/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍኤም 103.8) በሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሴኔጋል ሱዳንን 3 ለ 1 በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቅላለች።

ምሽት 1 ሰዓት ላይ በተካሄደው የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ሴኔጋል ፓፔ ጉዬ (ሁለት) እና ምባዬ ባስቆጠሯቸው ሶስት ግቦች ሱዳንን አሸንፋለች።

ሱዳን ከሽንፈት ያልታደጋትን ብቸኛ ግብ አሚር አብደላህ ከመረብ አሳርፏል።

ጨዋታው ምሽት 4 ሰዓት ላይ ቀጥሎ ሲካሄድ ማሊ እና ቱኒዚያ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል።