ማሻ፣ ታህሳስ 22/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍኤም 103.8) በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ የመጨረሻ ጨዋታ አልጄሪያ እና ቡርኪና ፋሶ አሸንፈዋል።
በምድብ አምስት ምሽት 1 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ በአልጀሪያ ኢኳቶሪያል ጊኒን 3 ለ 1 አሸንፋለች።
የአልጀኢሪያን የማሸነፊያ ግቦች ኢብራሂም ማዛ፣ ፋሬስ ቻይቢ እና ዚነዲን ቤላይድ ሲያስቆጥሩ ኤሚሊዮ ንሱ የኢኳቶሪያል ጊኒን ብቸኛ ግብ ከመረብ አገናኝቷል።
እንዲሁም በተመሳሳይ ሰዓት በተደረገው ጨዋታ ቡርኪና ፋሶ ሱዳንን 2 ለ 0 ማሸነፍ ችላለች።
በጨዋታው ላሲና ትራኦሬ እና አርሴን ኩዋሲ የቡርኪናፋሶን ግቦች አስቆጥረዋል።
ምድቡን አልጄሪያ ዘጠኝ ነጥብ በመያዝ ስታጠናቅቅ ቡርኪና ፋሶ በስድስት ነጥብ 2ኛ ደረጃን በመያዝ ጥሎ ማለፉን ተቀላቅለዋል።
ምሽት 4 ሰዓት ላይ የምድብ ስድስት ጨዋታዎች ቀጥለው ሲካሄዱ ጋቦን ከኮትዲቯር እንዲሁም ሞዛምቢክ ከካሜሩን ይጫወታሉ።
More Stories
አርሰናል ከ20 ዓመት በኋላ በሻምፒዮንስ ሊግ ለፍጻሜ ደረሰ
ማንቼስተር ዩናይትድ ሊቨርፑልን በማሸነፍ የሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎውን አረጋገጠ
ኬንያዊው አትሌት በሽልማት ተንበሸበሸ