ማሻ ፣ የግንቦት 11፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን በካንሰር ህመም መጠቃታቸውን ጽ/ቤታቸው አስታውቋል።
የ82 አመቱ ጆ ባይደን በከባድ የፕሮስቴት ካንሰር መጠቃታቸውና በካንሰር የተጠቃው ህዋሳቸው ወደ አጥንታቸው መዛመቱ ተነግሯል።
የፕሬዚዳንቱ የካንሰር ደረጃ ከፍ ያለ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፥ በሚደረግላቸው የህክምና አማራጮች ዙሪያ ከቤተሰቦቻቸው ጋር እየመከሩ ነው ሲል አሶሺየትድ ፕረስ ዘግቧል።
የወቅቱ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለጆ ባይደን ባስተላለፉት መልዕክት፥ በሁኔታው ማዘናቸውን ገልጸው ከህመማቸው በፍጥነት እንዲያገግሙ ተመኝተዋል።
ፋና
More Stories
የአውሮፓ ህብረት ያወጣቸውን ደንቦች መሠረት በማድረግ የግብርና ምርቶች ከደን ጭፍጨፋ ነፃ ሆነው እንዲመረቱ ከማድረግ አንፃር የግብርና ባለሙያዎች ሚና የጎላ እንደሆነ ተገለፀ ።
ትራምፕ ቲክ ቶክን የሚገዙ የአሜሪካ ባለሀብቶች ማግኘታቸውን ገለፁ
ሩሲያ እና ህንድ በጦር መሳሪያ አቅርቦት ላይ ያላቸውን ትብብር ለማሳደግ እንደሚሰሩ አስታወቁ፡፡