ማሻ ፣ የግንቦት 12፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በሩሲያ እና ዩክሬን የሰላም ጉዳይ ላይ በስልክ ከተወያዩ በኋላ ፑቲን ጦርነቱን ማቆም እንደሚፈልጉ እና ይህንንም ከውይይታቸው መረዳት እንደቻሉ ገልጸዋል፡፡
“ጦርነቱ እንዲቆም ፕሬዚዳንት ፑቲንን ጠይቄያቸዋለሁ፤ እርሳቸውም ይህ ደም አፋሳሽ ጦርነት እንዲያበቃ እንደሚፈልጉ ነግውኛል” ሲሉ ጉዳዩን አስመልክቶ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል፡፡
ስለ ዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ የተናገሩት ዶናልድ ትራምፕ “ዘለንስኪ ጠንካራ ሰው ነው፤ እሱም ይህ ጦርነት እንዲያበቃ ይፈልጋል” ብለዋል ሲል የዘገበው አናዶሉ ነው፡፡
ሩሲያ እና ዩክሬን በቫቲካን የተኩስ አቁም ውይይት ቢያደርጉ ጥሩ ይሆናል ያሉት ዶናልድ ትራምፕ፤ በቫቲካን ያለው የተረጋጋ ሁኔታ ለሰላም ንግግሩ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል ብለዋል፡፡
ኢቢሲ
More Stories
እየተጠናከረ የመጣው የብሪክስ ሀገራት ግንኙነት…
አሜሪካ ሶሪያን አጠቃች
የሩሲያ ጦር በፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን መኖሪያ ቤት ላይ ተፈጽሟል ላለው ጥቃት አፀፋ በዩክሬን ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት መፈጸሙን አስታውቋል።