መጋቢት 24፣ 2017 ግንባታው ሊጠናቀቅ ለተቃረበው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ ቀረበ፡፡
ታላቁ የሕዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት፤ ለኢትዮጵያውያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያን እና ለኢትዮጵያ ወዳጆች የግድቡ ግንባታ መሠረተ-ድንጋይ ለተቀመጠበት 14ኛ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፏል፡፡
በመልዕክቱም፤ የግድቡ ግንባታ ለፍጻሜ መቃረቡን በማኅበራዊ ትሥሥር ገጹ አስታውቋል፡፡
ግድቡ በመላው ሕዝብ ሁለንተናዊ ድጋፍ እየተከናወነ መሆኑ፣ ግንባታውም አንድነትን ማጠናከሩ፣ በደማቅ የዲፕሎማሲ ድል ታጅቦና የኢትዮጵያን ገፅታ በመገንባት ዘንድሮ 14ኛ ዓመቱን መያዙም ተጠቅሷል፡፡
ለዚህ ድል የበቃነው በኅብረት ችለን በመቆማችን ነው ያለው ጽሕፈት ቤቱ፤ ለሌሎችም ሀገራዊ ጉዳዮች የበለጠ በጋራ መቆም እንዳለብን ለእኛም ትምህርት ለዓለምም ምሳሌ ነው ብሏል፡፡
የሚደረገው ሁሉን አቀፍ ድጋፍም ግንባታው እስከሚጠናቀቅ ድረስ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርቧል፡፡
(ኤፍ ኤም ሲ)
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች