May 6, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

3ኛው የፓርላማ ዜጎች ፎረም እየተካሄደ ነው

ማሻ ፣ የመጋቢት 26፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) ሦስተኛው የፓርላማ የዜጎች ፎረም “ሕገ መንግሥትና ሕገ መንግሥትታዊነት በኢትዮጵያ” በሚል መሪ ሐሳብ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እየተካሄደ ነው፡፡

በውይይቱ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ታገሰ ጫፎ፣ በምክር ቤቱ የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር)፣ የምክር ቤት አባላት፣ ምሁራንና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

የኢትዮጵያ እና የዓለም ሕገ-መንግሥቶች የታሪክ ጉዞ ላይ ያተኮሩ ጽሑፎችም በፎረሙ ላይ ቀርበው ምክክር እየተደረገ መሆኑን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መረጃ አመላክቷል፡፡

ኢቢሲ