ማሻ ፣ የመጋቢት 24፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) ይህን የገለፁት የሸካ ዞን ልዩ የአዳሪ ትምህርት ማስጀመሪያ መረሃ ግብር ሁሉም ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በቴፒ ከተማ በተካሄደበት ወቅት ነው።
የመመዘኛ ፈተና አልፈው በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ልዩ አዳር ትምህርት ለመማር ከመጡት ተማሪዎች መካከል አንዳንዶቹ እንደገለፁት ይህ አድል መፈጠሩ የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ ተወዳዳሪ እንድሆኑ እንደሚያግዛቸው ነው ።
ትኩረታችን በተሻለ እውቀት ወደ ተሻለ ደረጃ መድረስ ነው ያሉት ተማሪዎቹ አሁንሥ በየደረጃው የሚገኙ ባለድርሻ አካላት ድጋፍና ክትትል ስራዎችን እንድያጠናክሩ ጠይቀዋል ።
የተማሪ ወላጆችም በበኩላቸው የዞን መንግሥትና በየደረጃው የሚገኙ አካላት ይህን እድል በማመቻቸቱ አመስግነው ልጆቻቸውን በተለየ መልኩ ክትትል እንደሚያደርጉ ገልጸዋል ።
ብቁና ተወዳዳሪ የሆኑ ተማሪዎችን ለማፍራት የአዳሪ ትምህርት ቤቶችን ማስፋፋት እንደሚያስፈልግ ተናግረው የዘርፉን ስራ ለመደገፍ የበኩላቸውን እንደሚወጡ ጠቁመዋል ።
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።