ማሻ ፣ የመጋቢት 24፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) ይህን የገለፁት የሸካ ዞን ልዩ የአዳሪ ትምህርት ማስጀመሪያ መረሃ ግብር ሁሉም ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በቴፒ ከተማ በተካሄደበት ወቅት ነው።
የመመዘኛ ፈተና አልፈው በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ልዩ አዳር ትምህርት ለመማር ከመጡት ተማሪዎች መካከል አንዳንዶቹ እንደገለፁት ይህ አድል መፈጠሩ የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ ተወዳዳሪ እንድሆኑ እንደሚያግዛቸው ነው ።
ትኩረታችን በተሻለ እውቀት ወደ ተሻለ ደረጃ መድረስ ነው ያሉት ተማሪዎቹ አሁንሥ በየደረጃው የሚገኙ ባለድርሻ አካላት ድጋፍና ክትትል ስራዎችን እንድያጠናክሩ ጠይቀዋል ።
የተማሪ ወላጆችም በበኩላቸው የዞን መንግሥትና በየደረጃው የሚገኙ አካላት ይህን እድል በማመቻቸቱ አመስግነው ልጆቻቸውን በተለየ መልኩ ክትትል እንደሚያደርጉ ገልጸዋል ።
ብቁና ተወዳዳሪ የሆኑ ተማሪዎችን ለማፍራት የአዳሪ ትምህርት ቤቶችን ማስፋፋት እንደሚያስፈልግ ተናግረው የዘርፉን ስራ ለመደገፍ የበኩላቸውን እንደሚወጡ ጠቁመዋል ።
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።