ለይፋዊ የስራ ጉብኝት በኢትዮጵያ የሚገኙት የእንግሊዟ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አንጄላ ሬይነር በሀገሪቱ መንግሥት የተራድኦ ድርጅት የተገዙ 12 አምቡላንሶችን ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር አስረክበዋል።
አምቡላንሶቹን የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ፕሬዚዳንት አበራ ቶላ ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሯ ተረክበዋል።
አምቡላንሶቹ ለእናቶችና ህፃናት አስቸኳይ ሰብዓዊ አገልግሎት የሚውሉ የህክምና ግብዓቶችን ያሟሉ መሆናቸውም ተመላክቷል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አንጄላ ሬይነር የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ሰብዓዊ ተግባራትን የጎበኙ ሲሆን ከማኅበሩ አመራሮች በትብብር በሚሰሯቸው ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል።
More Stories
ዓለምን እያነጋገረ ያለው ‘ሀንታ ቫይረስ’
የልማት ፍሬ፤ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በንጹሕ መጠጥ ውኃ አቅርቦት የታየው ታሪካዊ እምርታ
ለወረርሽኝና ለድንገተኛ አደጋ የማይበገር የጤና ስርዓት ለመዘርጋት የጤና ዘርፍ አገልግሎትና አስተዳደር ማሻሻያ ሪፎርምን በሙሉ አቅም ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ የክልሉ ጤና ቢሮ ገለፀ።