ለይፋዊ የስራ ጉብኝት በኢትዮጵያ የሚገኙት የእንግሊዟ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አንጄላ ሬይነር በሀገሪቱ መንግሥት የተራድኦ ድርጅት የተገዙ 12 አምቡላንሶችን ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር አስረክበዋል።
አምቡላንሶቹን የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ፕሬዚዳንት አበራ ቶላ ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሯ ተረክበዋል።
አምቡላንሶቹ ለእናቶችና ህፃናት አስቸኳይ ሰብዓዊ አገልግሎት የሚውሉ የህክምና ግብዓቶችን ያሟሉ መሆናቸውም ተመላክቷል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አንጄላ ሬይነር የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ሰብዓዊ ተግባራትን የጎበኙ ሲሆን ከማኅበሩ አመራሮች በትብብር በሚሰሯቸው ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል።
More Stories
ከ90 በላይ ኩባንያዎች የሚሳተፉበት ዓለም አቀፍ አውደርዕይ ሊካሄድ ነው
ኤች አይ ቪ ኤድስን በመከላከልና በመቆጣጠር በዜጎች ማህበራዊ ሕይወት ላይ ተጽእኖ እንዳያሳድር በማድረግ ክልላዊና ሀገራዊ ግቦችን ማሳካት እንደሚገባ ተገለፀ ።
ሕፃናት ወደ አፋቸው የሚያስገቧቸው ባዕድ ነገሮች እስከ ሞት ለሚያደርስ አደጋ እያጋለጣቸው ነው፦ የሕፃናት ቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስት