በአሜሪካ ሁለተኛ ትልቅ ከተማ በኾነችው ሎስ አንጀለስ አካባቢ ሰሞኑን የተቀሰቀሰው ሰደድ እሳት እስከ አኹን የ24 ሰዎችን ሕይወት ቀጥፏል። 13 ሰዎች የት እንደደረሱ አልታወቀም። እስከ አኹን 12 ሺሕ የሚኾኑ ቤቶችን አውድሟል። አንዳንድ መንደሮችን ወደ አመድነት የቀየረው ሰደድ እሳት፣ የፈጥረው ውድመት፣ እጅግ አስደንጋጭ ኾኗል።
የእሳት አደጋ ሠራተኞች አኹንም እሳቱን ለመቆጣጠር ብርቱ ጥረት ማድረጋቸውን ቀጥለዋል። እሳቱን ያባባሰው ደረቅ ነፋስ ተመልሶ ሊመጣ ይችላለ የሚል ስጋትም ተፈጥሯል።(VOA)
More Stories
አሜሪካ በኢራን ላይ የአየር ጥቃት ፈፀመች
አሜሪካ በኢራን ላይ አዲስ የአየር ጥቃት ፈፀመች
በ24 ሰዓት ውስጥ 25 መርከቦች በሆርሙዝ ሰርጥ አልፈዋል – ኢራን