በአሜሪካ ሁለተኛ ትልቅ ከተማ በኾነችው ሎስ አንጀለስ አካባቢ ሰሞኑን የተቀሰቀሰው ሰደድ እሳት እስከ አኹን የ24 ሰዎችን ሕይወት ቀጥፏል። 13 ሰዎች የት እንደደረሱ አልታወቀም። እስከ አኹን 12 ሺሕ የሚኾኑ ቤቶችን አውድሟል። አንዳንድ መንደሮችን ወደ አመድነት የቀየረው ሰደድ እሳት፣ የፈጥረው ውድመት፣ እጅግ አስደንጋጭ ኾኗል።
የእሳት አደጋ ሠራተኞች አኹንም እሳቱን ለመቆጣጠር ብርቱ ጥረት ማድረጋቸውን ቀጥለዋል። እሳቱን ያባባሰው ደረቅ ነፋስ ተመልሶ ሊመጣ ይችላለ የሚል ስጋትም ተፈጥሯል።(VOA)
More Stories
የአሜሪካ ወታደሮች ላይ የተሰነዘረውን የጥቃት ሙከራ ተከትሎ ዋሽንግተን ኢራን ላይ “ከፍተኛ” ጥቃት ፈጸመች
አሜሪካ በኢራን ጦርነት ከ37 ቢሊየን ዶላር በላይ እንዳወጣች ተገለፀ::
አሜሪካ የመርከቦችን እንቅስቃሴ እያወኩ ነው ባለቻቸው የኢራን ወታደራዊ ኢላማዎች ላይ አዲስ ጥቃት ፈጸመች፡፡