ከትምህርት ሚኒስቴር ዓበይት የሪፎርም ትኩረቶች አንዱ የስርዓተ ትምህርት ሪፎርም ነው።አዲሱ ስርዓተ ትምህርት አንድ ተማሪ 3 ቋንቋዎችን እንዲናገር የሚያስችል መሆኑን በሚኒስቴሩ የተፈጥሮ ሳይንስ ስርዓተ ትምህርት ዝግጅት ኃላፊ ዛፏ አብርሃ ለኢቢሲ ገልፀዋል።ተማሪዎች በቅድመ አንደኛ ደረጃ በአፍ መፍቻ ቋንቋ፣ በአንደኛ ደረጃ ዓለም አቀፍ ቋንቋ ማለትም እንግሊዝኛ ከዚያም ከ3ኛ ክፍል በኋላ ሌላ የአጎራባች ክልል ቋንቋ እንደሚማሩ ኃላፊዋ አስረድተዋል።የአጎራባች ክልል ቋንቋውም በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሳይሆን በክልሎች የሚመረጥ እንደሆነም ነው የገለፁት።
EBC
More Stories
ሮቦቶችም ተማሪ ሆኑ! በቻይና የተከፈተው የዓለማችን መጀመሪያው የሮቦቶች ትምህርት ቤት አስገራሚ እውነታ
የግል ጄታቸውን ለሕዝብ አምቡላንስ አገልግሎት የለገሱት ጋናዊው ቱጃር
ፌራሪ የመጀመሪያውን ባለ 5 መቀመጫ የኤሌክትሪክ መኪና አስተዋወቀ