የሸካ ዞን ምክር ቤት 5ኛ ዙር 11ኛ ዓመት የስራ ዘመን 21ኛ መደበኛ ጉባኤውን በቴፒ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል።ጉባኤውን በመክፈቻ ንግግር ያስጀመሩት የዞኑ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ ዮሐንስ ካሳሁን በ2016 በጀት ዓመት በዞኑ በርካታ ተግባራት በተሻለ ደረጃ የተፈፀሙ በመሆናቸውን ለዚህም ስኬት የአስፈጻሚ አካላትና በየደረጃው የሚገኙ ባለድርሻ አካላት ሚና ከፍተኛ ነው ብለዋል።ዋና አፈጉባኤው አያይዘውም ምንም እንኳን አመርቂ ተግባራት በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ ቢሆንም አሁንም ሰፊ ርብርብና ትኩረት የሚጠይቁ ጉዳዮች መኖራቸውን ጠቁመዋል።ጉባኤዉ ለ2 ተከታታይ ቀናት የሚቀጥል ሲሆን የአስፈጻሚ አካላት የ2016 በጀት ዓመት አፈጻጸም ሪፖርትን ጨምሮ የዞኑ የ2017 ጥቅል በጀት እና ሌሎችም የተያዙ አጀንዳዎች ዙሪያ በመወያየት ምክር ቤቱ ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
የሸካ ዞን ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ማካሄድ ጀመረ
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።