የሸካ ዞን ምክር ቤት 5ኛ ዙር 11ኛ ዓመት የስራ ዘመን 21ኛ መደበኛ ጉባኤውን በቴፒ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል።ጉባኤውን በመክፈቻ ንግግር ያስጀመሩት የዞኑ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ ዮሐንስ ካሳሁን በ2016 በጀት ዓመት በዞኑ በርካታ ተግባራት በተሻለ ደረጃ የተፈፀሙ በመሆናቸውን ለዚህም ስኬት የአስፈጻሚ አካላትና በየደረጃው የሚገኙ ባለድርሻ አካላት ሚና ከፍተኛ ነው ብለዋል።ዋና አፈጉባኤው አያይዘውም ምንም እንኳን አመርቂ ተግባራት በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ ቢሆንም አሁንም ሰፊ ርብርብና ትኩረት የሚጠይቁ ጉዳዮች መኖራቸውን ጠቁመዋል።ጉባኤዉ ለ2 ተከታታይ ቀናት የሚቀጥል ሲሆን የአስፈጻሚ አካላት የ2016 በጀት ዓመት አፈጻጸም ሪፖርትን ጨምሮ የዞኑ የ2017 ጥቅል በጀት እና ሌሎችም የተያዙ አጀንዳዎች ዙሪያ በመወያየት ምክር ቤቱ ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
የሸካ ዞን ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ማካሄድ ጀመረ
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች