የሀገር መከላከያ ሠራዊት የሀገርን ሉዓላዊነት እና ሰላም ከማረጋገጥ ባለፈ በልማቱ ላይ እያደረገ ያለው ተሳትፎ አበረታች ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር ) ገለጹ፡፡ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር ) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ እንደገለጹት ÷መከላከያ ሠራዊት የሰላም ምንጭ ብቻ ሳይሆን የልማት እና የፈጠራ ምንጭ መሆን ስላለበት በዚህ አግባብ እየተመራ እየተገኘ ያለው ውጤት ተስፋ ሰጭ ነው ፡፡ይህም ተስፋ ሰጭ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል ነው ያሉት ።በስንዴ ምርት በእርሻ በ #አረንጓዴዓሻራ ብዙ የኢንዱስትሪ ውጤቶችን በማምረት ልማቱን ለማሳለጥ እና የብልፅግና መሰረት ለመጣል እያደረገ ያለው ጥረት ሊበረታታ እንደሚገባም ገልጸዋል፡፡
FBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች