በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ከታክስ ዕዳ ከ49 ቢሊየን ብር በላይ መሰብሰቡን ገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
ከታክስ ዕዳ 41 ቢሊየን 662 ሚሊየን 896 ሺህ 213 ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 49 ቢሊየን 664 ሚሊየን 299 ሺህ 370 ብር መሰብሰቡን ሚኒስቴሩ አስታውቋል፡፡
ከፍተኛ የታክስ ዕዳ መጠን ያለባቸውን ታክስ ከፋዮች በመለየት ቅድሚያ ተሰጥቶ መሠራቱና ለዋና መስሪያ ቤት በልዩ ሁኔታ እንዲታዩ የሚቀርቡ ጥያቄዎችን ፈጥኖ ምላሽ መስጠቱ ለዕቅዱ መሳካት ማገዙ ተገልጿል፡፡
ከተሰበሰበው የታክስ ዕዳ ውስጥ 30 ቢሊየኑ 30 ቀን ካልሞላው የታክስ ዕዳ መሰብሰቡን የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል፡፡
FBC
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።