በፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር የተመራ ልዑክ ሩሲያ ገብቷል፡፡
ልዑኩ ለብሪክስ አባል ሀገራት በሴንት ፒተርስበርግ ከተማ በተዘጋጀው ፓርላሜንታዊ ዓመታዊ ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ ነው ሩሲያ የገባው፡፡
ጉባዔው ሐምሌ 4 እና 5 ቀን 2016 ዓ.ም የሚካሄድ ሲሆን÷በዛሬው ዕለት የብሪክስ አባል ሀገራት በተለያዩ የባለ ብዙ ወገን የግንኙነት ርዕሰ ጉዳዮች ላይ መምከራቸው ተጠቅሳል፡፡
በጉባዔው የአባል ሀገራቱን ትብብር እና ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር የሚረዳ ፕሮቶኮል እና በጋራ ለመሥራት የሚረዳ ስምምነትም መፈረሙ ተጠቁሟል፡፡
በመድረኩ ላይ የኢትዮጵያን ፓርላማ አቋም እና የግንኙነት ዝግጁነትን በተመለከተ በአፋ-ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር ገለጻ መደረጉን የፌደሬሽን ምክር ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡
የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት፣ የፓርላሜንታዊ ዲፕሎማሲ፣ ቀጣይነት ያለው እድገት፣ ዘላቂ ሰላም እና ደህንነት ትኩረት የሰጡባቸው ነጥቦች ናቸው ተብሏል፡፡
አፈ-ጉባዔ አገኘሁ በዚሁ ወቅት÷ የኢትዮጵያ ፓርላማ የተሳታፊነት ብቻ ሳይሆን የመሪነት ሚናውን ጭምር በብቃት እንደሚወጣ አመላክተዋል፡፡
መድረኩ በሁለት ቀናት ውሎው በእነዚህና በሌሎች ርዕሳነ ጉዳዮች ላይ መክሮ ቀጣይ አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።
FBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።